ለ አእምሮ / Le'Aimero ለ አእምሮ የጥር 2006 / January 2014/ እትም፣ ቅጽ 2 ቁጥር 6 | Page 55

(የላይኛው ሰነድ እንደገና ሲጻፍ) የተላከ ከእቴጌ ጥይቱ ብረሃነ ዘኢትዮጵያ ይድረስ ከማህበረ ዲር ሥልጣን ወደብረ ገነት ዘኢየሩሳሌም። እንዴት ሰንብታችኀል። እኔ እግዚአብሔር ይመስገን ደህና ነኝ። እናንተ ብትስማሙ እርስ በርሳችሁ ብትፋቀሩ አንድነታችሁን ብታጸኑ ይሻልል እንጂ ትግሬ የብቻው ነው ሸዋ የብቻው ነው ቢገምድር ጎጃም የብቻው ነው እያላችሁ ጎሣ እየለያችሁ ብትጣሉ ምን ትረባላችሁ። እኛስ በኢየሩሳሌም ነገር ይህን ያህል መድከማችን ያንን ያህል ብር ባንክ አግብተን የዚያን ወለድና አቤቱ የሚወጣውን ክራይ መስጠታችን እንዳትቸገሩ የሰው ፊት እንዳታዩ ያንን እየበላችሁ ለኛም የጌታችን ደም ከፈሰሰበት ላይ ዳዊት እብድትደግሙልን እንድታዝኑልን እናንተም ፩ ነታችሁን እንዲጸና ብለን ነው እንጅ ገንዘቡ ተርፎ ባገራችን በኢትዮጵያ ለምንሰጠው ሰው አጥተን አይደለም።አሁንም ስለ እግዚአብሔር ብላችሁ እናንተም እርስ በእርሳቸሁ ተፋቀሩ ለኛም ዳዊት ድገሙልን እዘኑልን ሳትቸገሩ እንዴት የድፍን አውሮፓ መሣቂያ ትሆናላችሁ። አሁንም ይኸው እማሆይ ወለተ ተክሌ መቃብሬ ከዚያውይሁን ብላ መጥታለችና አደራችሁን በምኑም በምኑም ነገር እንዳታስቀይሟት። እንግዲህ ሷ እንዲህ አደረጉኝ ብላ የላከብችን እንደሆን እናንተንም እጠላችኀለሁ።እኔንም እንዳስትቀይሙኝ። 29 ቀን 1900 ዓመት አዲስ አበባ ከተማ ተጻፈ *** መልዕክቱ በነገር አሁን ለተሳከረውና ለማይደማመጠው ትውልድ የተጻፈ ይመስላል 55