ለ አእምሮ / Le'Aimero ለ አእምሮ የጥር 2006 / January 2014/ እትም፣ ቅጽ 2 ቁጥር 6 | Page 13

አንደኛው የጆርጅ ኦርቭል ድርሰት ነው። የእሱ „…የእንስሳት እርሻ „ የሚለው አጭር ልበ ወለድ ድርሰቱ ግሩምና ድንቅ ጽሑፍ ነው። „…አያ ጅቦ ሳታመከኝ ብላኝ“ ያላቸው የአህያዋ አነጋገር ከነተረቱ እንደዚሁ ሌላው የሚጠቀስ ምሳሌ ነው ። ፊታውራሪ ተክለ ሐዋሪያት የመጀመሪያ ድርሰታቸውን በቲያትር መልክ ጽፈውና አዘጋጅተው አዲስ አበባ ላይ በዘመናቸው መድረክ ላይ ያቀረቡት ጨዋታ በዚሁ በፋቡላ በእንስሶች ታሪክ ላይ የተመሰረተ ነው። ለ ሰልችቶት ይመስላል ወይም ተናዶ ወይም ደግሞ ድክመትና ጥንካሬአቸውን በሁለቱም ወገን መካከል ያለውን ለማወቅ ከአለው ፍላጎትና ጉግት ተነስቶ ሊሆን ይችላል ይህኛው አውራ ውሻ ስብሰባ የጠራበት ዋናው ምክንያት የትኛው እንደሆነ አይታወቅም። ወይስ ውሸትና እውነት ተለይቶና ተበጥሮ እንዲወጣ ፈልጎ ይሆን? ያ ውሻ የመንደሩን ውሾች ሁሉ ጠርቶ እንደገና ለሦስተኛ ጊዜ „…እስቲ ንገሩኝ …ምንድነው እነሱ ያላቸው ጥንካሬ እኛ ደግሞ የሌለን?“ ማለቱ ከዚህ ሁሉ አመት በሁዋላ -አጥንት ከአዩ ብዙ አመታቸው ነውየገርማል። አጥንቱ ት