ለ አእምሮ / Le'Aimero ለ አእምሮ ሚያዝያ 2006 / April 2014 / እትም፣ ቅጽ 2 ቁጥር 08 | Page 27
ተገዢው ክፍል ዝም ቢል እነሱን መርተው ሥልጣኑን ለመንጠቅ
የሚፈልጉት ክፍሎች እሳት ከመለኮስ አይመለሱም። ገዢውም ደህና
እንቅልፍ ሳይወስደው ሁሌ እንደቃዣ -ከአሁን አሁን መጥተው አነቁኝ
ብሎ በሰቀቀን የሚኖር ነው። እንደዚህ ዓይነቱ አስተዳደር መገላመጥ
ያበዛል። የእራሱን ጥላ እንኳ ሲያይ ይደነግጣል። እንደ ተደበቀ
እንተቅበዘበዘ እንደ ተጣደፈና ከሰው እንደራቀ አንድ ቀን ሳይደላው
እፎይ ብሎ ሳያርፍና የ