ለ አእምሮ / Le'Aimero ለ አእምሮ ልዩ እትም / ታህሳስ/ጥር 2006 / 01 / 2014 – አዲስ ዓመት | Page 6

„….ቅመሱት እኛም ቀምሰነው ወጥቶልናል …..ይገባችሁዋል „ የሚሉት የቀድሞ ም ሥራቅ ጀርመን ወዳጆቻችን… ሁለቱም ሦስቱም ወቃሾች ሁሉም በእኛ ላይ በሚሰጡት „ፍርድ“ ዕውነት ያዘለ ነገር የወረወሩ ይመስለናል። ዕውነትም አላቸው። „…የሰላምና የፍቅር፣የደስታና የጤና የብልጽግና እና የጥጋብ የጸጋና የሐብት…“ ምኞቶችን ከልብ ታስቦበት ለዘመድ ወይም ለወገን ከአልተመኙላቸው፣ያ ነገር ዝም ብሎ ከተፍ አይልም። መመኘት ብቻ ሳይሆን ያ የተመኙት እንዲመጣም እንዲደርስም በፍቅርና በአንድነት በጋራ አንድ ላይ ሁነው ተረዳድተው ተግተው ጥረው ደክመው እንደገና በጋራ ያ ሁኔታ እንዲመጣ ከአልሰሩበት እንዲያው ከሰማይ ዱብ የሚል የመና ዳቦም አይደለም። ተረግመን ለማኝ ሆነን እንድንቀር የተደረግን ፍጡሮችም“ አይደለንም። ቁም ነገሩ ያለው ሌላ ቦታ ላይ ነው። እነሱ ፣- ይህ ነው የኑሮ ብልሃቱ- እነሱን ከሚያጣላና ጥላቻን ብቻ ከሚያስተምር አይዲዎሎጂ እና የፖለቲካ ቲዎሪ እረሳቸውን አርቀው ተቻችለውና ተከባብረው -እኛ ሁላችንም በየአመቱ አንዴ ወይም ሁለቴ እንደምንለው „…የሰላ