Christian Books & Magazines - Free Berea Magazine 5 | Page 38
እዛም ቤት እሳት አለ
ከእህት ለምለም የኋላእሸት
ቤተሰብ በአምላካችን በእግዚአብሔር በኤደን ገነት
ውስጥ የተመሰረተ፥ የመጀመሪያው ተቋም ነው:: በመጽሐፍ
ቅዱሳችን ውስጥ ዘፍጥረት 1 (27-28) እንደተጻፈው
እግዚአብሔር ቤተሰብን ሲያይ የሚያየው ባልና ሚስቱን፤
ከዛም ልጆቻቸውን፥ ብሎም ቀጣዩን ትውልዳቸውን ነው::
ስለዚህ ትውልድ የሚጀምረው ከቤተሰብ ነው ማለት ነው::
እንደ እግዚአብሔር ሃሳብ የተባረከ ትውልድ ለማፍራት
የሚቻለው ደግሞ፥ ልጆች በአባትና በእናት ስር በፍቅርና
በስነስርዓት ተኮትኩተውና ታንፀው ሲያድጉ ነው::
ነገር ግን ይሄ የእግዚአብሔር ተቋም(ቤተሰብ)፥
በተለይም ወላጅነት፥ ከፍተኛ ተግዳሮት እንደገጠመውና
አሳዛኝና አስቸጋሪ ቦታ ላይ እንደሚገኝ ይታያል:: ለዚህም
ምክንያቱ፥ ወላጆች እግዚአብሔር በቃሉ እንዳዘዘን ዘፍጥረት
18(19) ልጆቻችንን የእግዚአብሔርን መንገድ ይጠብቁ
ዘንድ አላስተማርናቸውምና ነው:: ስለዚህ ይሄ ትውልድ
በከፊል እግዚአብሔርን የማያውቅና የማይፈራ፥ ግብረገብነት
የጎደለው፥ ወላጆችን የሚያሳዝንና የጥፋትን ጎዳና የተከተለ
ሆኗል::
ኖሮን ሊሆን ይችላል::
ነገሩን ብናስተውለው ግን የደረሱበት ሥልጣኔና
የሚኖሩበት በረከት፥ የአባቶቻቸው አምላክ እግዚአብሔር
ከለቀቀላቸው ታላቅ ምህረት የተነሳ ነው ብዬ አምናለሁ::
ምክንያቱም የቀደሙት አባቶቻቸው ወደዚች ምድር
የመጡት፥ በነፃነት ጌታን ለማምለክ ፈልገው ስለነበረ፤ ጌታ
የሰጣቸውን ይችን ምድር፥ ራሳቸውንና ትውል