Christian Books & Magazines - Free Berea Magazine 5 | Page 36

ከአትላንታ ኮንፍረንስ ትዝታዎች 4ተኛውን የቤርያ ዓመታዊ ኮንፍራንስ ያደረግነው፤አምና ጁን 2015 በአትላንታ ከተማ በምትገኘው የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተርክርስቲያን ነበር:: በኮንፍራንሱ ላይ የተገኛችሁ ሁሉ እግዚአብሔር መልካም ጊዜ እንደሰጠን ምስክሮች ናችሁ:: ክብር ሁሉ ሁሉን ላደረገው ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ይሁን:: የቤርያ አመታዊ ኮንፍራንስ የሚደረግባቸው ቀኖች፤ ዓርብ ቅዳሜና እሁድ ናቸው:: ነገር ግን ሐሙስ ማታ ኮንፍራንሱን ለማዘጋጀት እድል የደረሳቸው ቅዱሳን የአቀባበል ምሽት ያደርጋሉ:: በዚህም መሰረት በአትላንታ የሚገኙ ቅዱሳንም ከሌላ ቦታ ለመጡ ወገኖች ሞቅና ደመቅ ያለ ቤተሰባዊ አቀባበል አድርገው ነበር:: ይህ ቀን በጣም ደስ የሚል ነው:: ቤተሰብ ብዙ ጊዜ ቆይቶ ሲገናኝ የሚታየው ደስታ በሁሉም ፊት ላይ የሚታይበት የመጀመሪያ ቀን፤ ከዛም ዓርብ ጠዋት መደበኛው ኮንፍራንስ ተጀምሮ እሁድ ማታ እስከሚያልቅ ድረስ......ጌታን አብረን አመለክን…..ቃሉን ተካፈልን…...ማእድን ቆረስን…. አዎ ሁሉንም አብረን:: ክብር ለኢየሱስ ይሁን:: መዝሙረ ዳዊት 133 1 ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ እነሆ፥ መልካም ነው፥ እነሆም፥ ያማረ ነው። ቅዱሳንን በመቀበል የተጋችሁ የአትላንታ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን ወገኖቻችን፥ እግዚአብሔር አምላክ በሚያስፈልጋችሁ ሁሉ ይባርካችሁ እንላለን:: በጌታ ፍቅር እንወዳችኋለን:: የዘንድሮው ኮንፍራንሳችን የሚካሄደው በአሜሪካ ዋና ከተማ በዋሽንግተን ዲሲ በምትገኘው በዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን ነው:: ይህንን የአንድነታችንን ጊዜ በዚህ ቤተክርስቲያን እንድናደርግ የፈቀዱልንን የቤተ ክርስቲያኑዋን ዋና መጋቢ:· ፓስተር ሐንፍሬ አሊጋዝን · ፓስተር የትናየት ኃይሌን · ፓስተር ጆርጅ ገላትያስን · ፓስተር አብተው ከበደን · ፓስተር አማኑኤል ኃይሌን፥ · የቤተ ክርስቲያኑዋን ሽማግሌዎች፥ አገልጋዮችና ምእመናኑን በሙሉ ጌታ ይባርካችሁ፥ እንዳከበራችሁንም እግዚአብሔር ያክብርልን እንላለን:: ወደ ሮሜ ሰዎች 12፥13 ቅዱሳንን በሚያስፈልጋቸው እርዱ፤ እንግዶችን ለመቀበል ትጉ። እግዚአብሔር ቢፈቅድና ብንኖር ጌታ የሚሰራውን ድንቅ ይዘን በሚቀጥለው መጽሔታችን እስከምንገናኝ የሰላም አምላክ ከሁላችን ጋር ይሁን፤ አሜን። ከመጽሔት ዝግጅት ክፍል:: 36