Christian Books & Magazines - Free Berea Magazine 5 | Page 30

የአካል ብልቱ የአካል ብልቱ አለመስማማቱ ቀርቶ አንድነቱ ቤተሰብነቱ አንዱ ያለ አንዱ ላይቆም ሙሉ ሆኖ አንዱ አካል ከሌላው ሲኖር ተጨካክኖ አንድኛው ካንደኛው አንድ ላይ ተጣብቆ አካል ላይለያይ ሀሳብ ተራርቆ እራስ ያለ አንገት ሁሉን ላይቃኝ ዞሮ መስራት ላይቻለው ያይንን ስራ ጆሮ አሽቶ ላይለየው አፍ እንደ አፍንጫ እፍንጫም እንደ አፍ ላይሆን ጣእም መስጫ ደካማ መሳዩ የአካሉ ክፍል ስንኩል ሊያረግ ሁሉን ታናሹ ቢጎድል ከዚያ ካንዱ መንፈስ ከውሃው ጠጥቶ አንዱን መንግስት ሊወርስ እዚህ ተገፋፍቶ ብቻውን ሊወጣ ሌላውን አጣጥሎ የሱን ፀጋ ሊያገን የወንድሙን ገድሎ ያንዱ አካል ብልቶች ምነው ተለያዩ ደርሰው እንደ ጠላት እንደዚህ ተያዩ የእግዚአብሔር ቤተሰብ .... ባላገር አድርጎት እንዳይሆን እንግዳ የገዛ ወንድሙን ሲያየው እንደባዳ አይ ብልት ሞኙ ሰው አንደኛው ያላንዱ ያየውን ላይወርሰው ሁሉን ለኔ ለኔ ለኔ ብቻ ብሎ ከገዛ ወገኑ ልቡን አስኮብልሎ። አፍንጫን ሲመቱት ላይቀር አይን ማልቀሱ ካንድ ዘር ተወልዶ አይ ሆድ መባባሱ ብቻውን ቢቀመጥ አካል ተገንጥሎ ከመጣል ላያመልጥ ከወገኑ ጎድሎ ካንደኛው ቢነጠል በሌላው ታጅቦ ጌታውን ላያመልክ አንድ እጅ አጨብጭቦ መለየትን ወዶ መሆን ሲሻ ሌጣ ተግባሩን ለብቻው ችሎ ላይወጣ መብራት ብርጭቆውን ወግድልኝ ቢለው ነፋስ መጥቶ ወዲያው እንደሚያጨልመው 30 ሁሉን ድንቅ አድርጎ ፈጣሪ አስውቦ መልክ ቢለያይም ባንድነት ሰብስቦ ብልቶችን ሁሉ አድርጎ ያንዱ አካል አንዱን ላንዱ ሰጥቶ ምንም እንዳይጎድል መስማት ብቻ ቢሆን አይን ሁሉ ታውሮ ጆሮ እያዳመጠ መውደቅ ተደናብሮ ባንዱ ያለውን ስራ ሌላው ላያሟላ እየተገፋፋ ብልት ሲጠላላ። በዚያ በሸለቆ አጥንት ደርቆ ደርቆ አንዱ አጥንት ካንዱ አጥንት እጅግ ተራርቆ ተስፋ ታጥቶባቸው በህይወት የማይኖሩ ዳግመኛ ተነስተው ነፍስን የማይዘሩ በእግዚአብሔር ቃል ትንቢትን ተናግሮ በመንፈሱ እስትንፋስ በህይወት አኑሮ አጥንትን ሲያለብስ ጅማትና ስጋ ትንፋሽን ሲሰጠው ቁርበት ሲዘረጋ በሰው ልጅ ተነግሮ ለንፋስ ትንቢቱ በህይወት እንዲኖሩ የተገደሉቱ መንፈሱ ሲመጣ ሲወርድ በላያቸው ታላቅም ሰራዊት አድርጎ አቆማቸው የተለያዩትን አጥንቶች ሰብስቦ አንድ ያረገው መንፈስ ሁሉን አቀራርቦ በእውነት በጸጋው በቃሉ አድሶ የጥልን ግድግዳ ዳግም አፈራርሶ አካል ጤና እንዲሆን ምንም ማይጎድለው ፈጣሪ ብልትን ራርቶ እንዲፈውሰው እየተዋደደ ሁሉ ተከባብሮ የአምላኩን ትእዛዝ ይፈፅም ተፋቅሮ ምስጋና እንዲበዛ ላምላካችን ክብር መቀራረብ እንጂ መለያየት ይቅር ። ከእህት ሃና ከበደ (ኢያኤል)